ፅዱ አዲስ አበባ ለአዲስ አመት

  • 'ፅዱ አዲስ አበባ ለአዲስ ዓመት' በሚል መሪ ቃል የፅዳት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን የየካ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ /ቤት አስታወቀ::
  • ህብረተሰቡ ከበአል ጋር ተያይዞ የሚፈጠረውን ቆሻሻ በአግባቡ ማስወገድ እንዳለበት ጥሪ ቀርቧል::

==============================================
"ፅዱ አዲስ አበባ ለአዲስ" አመት በሚል መሪ ቃል የፅዳት ዘመቻ እየተደረገ መሆኑን የየካ ክፍለ ስራ አስወቀ:: የፅዳት መርሀ ግብሩ ጳጉሜ 1 መጀመሩንና እስከ መስከረም 4 እንደሚቆይ ተገልፇል::

የከፍለ ከተማው ዋና ስራ አስኪያጅ / ወሰኔ በየነ ከማህበራዊ ሚዲያችን ጋር ባደረጉት ቆይታ ክፍለ ከተማችን ለስራና ለኑሮ ምቹና ማራኪ ለማድረግ በሁሉም ወረዳዎች : ቀጣናዎችና መንደሮች እንዲሁም ተቋማት ቆሻሻ ያለአግባብ እንዳይጣል ለማድረግ የሚያስችል ንቅናቄ መሆኑን ገልፀዋል::


አሮጌ ነገራችንን አፅድተን አዲሱን አመት በአዲስ መንፈስ መቀበል አለብን ያሉት / ወሰኔ ህብረተሰቡ የአካባቢውን 50 ሜትር ራዲየስ እንዲያፀዳ : በአልን ተከትሎ የሚፈጠረውን ቆሻሻ በአግባቡ እንዲያስወግድና ከመንግስት ጉትጎታ እና ዘመቻ ወጥቶ ፅዳትን ባህሉ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል::

በትምህርት ቤቶች : በሆስፒታሎችና የሀይማኖት ተቋማት ዘመቻው መጀመሩን ጠቅሰው ከክረምት ወደ በጋ ሽግግር የሚደረግበት ወቅትም በመሆኑ የክፍለ ከተማው ህዝብ ራሱን ከተላላፊ በሽታዎች እንዲጠብቅ ሀላፊዋ አሳስበዋል::

ተቋሙ በቀጣይ በጀት አመት የህብረተሰቡን የፅዳት ባህል ማሳደግ እና ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም የክፍለ ከተማውን ገፅታ መገንባት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ / ወሰኔ ተናግረዋል::


Comments

Popular posts from this blog

የደመወዝ ስኬል አፈጻጸም መመሪያ

በዜሮ ዓመት የወጣ ክፍት የስራ ማስታወቂያ

የነጥብ ስራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ጥናት