በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጠ፡፡

 “ህገ-ወጥ የሠዎች ዝውውር ወንጀልን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው፡፡” 





ህጋዊ የሰዎች ዝውውር የስራ ኃይል ወደ ውጭ ሃገር በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ፣ የስራ አጥነት ችግርን ለመቀነስ ፣ የላቀ ቴክኖሎጂንና እውቀትን ለማሸጋገር እና የአገር ውስጥ ምርትን ወደ ውጭ ለመላክ የጎላ ጥቅም ቢኖረውም ህገ-ወጥ ሲሆን ግን በዜጎችና በሐገር ገፅታ ላይ የከፋ ጠባሳ ጥሎ ያልፋል፡፡

የየካ ክ/ከተማ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች ፣ ለአረጋውያን ፣ ለወጣትና ሴት አደረጃጀት አመራሮች በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ሰዎን በህገ ወጥ መንገድ የማዘዋወር ወንጀል ሰዎችን በማስፈራራት ፤ ሀይልን ወይም ሌላ ዓይነት መንገድን በመጠቀም በጠለፋ ፣ በማታለል ፣ በማሳሳት ፣ ስልጣንን ወይም የሰዎችን ለወንጀሉ ተጋላጭነት በመጠቀም የሚፈፀም ህገወጥ ድርጊት መሆኑ በመድረኩ ተብራርቷል፡፡


ድህነተ ፣ ስራ አጥነትና የተሸለ ህይወት ፍለጋ የህገ ወጥ ዝውውር ምክንያች በመሆናቸው በነዚህ ችግሮች ዙሪያ መስራት እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል፡፡ ህብረተሰቡም የህገ-ወጥ ድርጊት ፈጻሚ አካላትን ማለትም ህገ-ወጥ ደላሎችን ፣ ህገ-ወጥ ድርጊት የሚፈፅሙ ህጋዊ ሽፋን ያላቸው ሰራተኛና ስራ አገናኝ ኤጀንሲዎችንና የንግድ ድርጅቶችን በጋራ መዋጋት ይኖርበታል ተብሏል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም  በመንግስት በኩል ተገቢውን አደረጃጀትና ቅንጅት መፍጠር ፣ ተከታታይነት ያላቸው የግንዛቤ ስራዎችን መስራት እና ህጋዊ የውጭ ሃገር ስራ ስምሪት አገልግሎትን ቀልጣፋና ውጤታማ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የስልጠና ሰነዱ ያስረዳል፡፡

Comments

Popular posts from this blog

የደመወዝ ስኬል አፈጻጸም መመሪያ

በዜሮ ዓመት የወጣ ክፍት የስራ ማስታወቂያ

የነጥብ ስራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ጥናት